EthiopiaPoliticsRegions

ማንነታቸው ያልታወቀ 40 የታጠቁ ወታደሮችን ይዞ ትግራይ ክልል የገባ አንቶኖቭ አውሮፕላን በመቀሌ አሉላ አባ ነጋ አውሮፕላን ማረፊያ ተያዘ።

ማንነታቸው ያልታወቀ 40 የታጠቁ ወታደሮችን ይዞ ትግራይ ክልል የገባ አንቶኖቭ አውሮፕላን በመቀሌ አሉላ አባ ነጋ አውሮፕላን ማረፊያ ተያዘ።

ምንጮች ለቢቢሲ እንደገለፁት በአውሮፕላኑ ውስጥ የነበሩት የታጠቁ ወታደሮች ተልዕኮና ማንነታቸው ባይታወቅም ኢትዮጵያዊያን እንደሆኑ ታዉቋል።
ከሁለት ቀናት በፊት ከሱዳን በኩል ወደ ኢትዮጵያ እንደገባ የተጠረጠረው አንቶኖቭ አውሮፕላንና አሳፍሯቸው የነበሩት 40 የታጠቁ ወታደሮች በመቀሌው የአሉላ አባ ነጋ አውሮፕላን ማረፊያ መያዛቸውን የክልሉ ደህንነት ምንጮች በአካባቢው ለሚገኘው የቢቢሲ ዘጋቢ ገልፀዋል።
ምንጮቹ ጨምረው ወታደሮቹ አንቶኖቭ ተብሎ በሚታወቀው ግዙፍ አውሮፕላን በአሉላ አባ ነጋ አየር ማረፊያ በድንገት ያረፉት በስህተት መሆኑን ገልፀው፤ የክልሉ ፖሊስ ጉዳዩን እየመረመረው እንደሚገኝ ተናግረዋል።

Related Articles

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Back to top button