EconomyEthiopiaRegionsSocial

በምስራቅ ጎጃም በደረሰ የመሬት መንሸራተት አደጋ የ8 ሰዎች ህይወት አለፈ፡፡

በምስራቅ ጎጃም ዞን ጎንቻ ሲሶ እነሴ ወረዳ በተከሰተ የመሬት መንሸራተት አደጋ የ8 ሰዎች ህይወት ማለፉን ፋና ዘግቧል።

ጎንቻ ሲሶ እነሴ ወረዳ የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት እንዳስታወቀው፥ አደጋው የደረሰው ነሃሴ ነሀሴ 8 ቀን 2010 ዓ.ም ከሌሊቱ 7 ሰዓት አካባቢ ነው።

በመሬት መንሸራተት አደጋውም የ8 ሰዎች ህይወት ሲያልፍ ስድስቱ የአንድ ቤተሰብ አባላት ሲሆኑ፥ ሁለቱ ደግሞ ስራ ለማገዝ ከሌላ ቦታ ወደ ስፍራው ያቀኑ ናቸው።

በአደጋው ከሰው ህይወት በተጨማሪ ቤት ከነሙሉ ንብረት፣ በአካባቢው የተዘራ ሰብል፣ አትክልትና ፍራፍሬ በሙሉ መውደሙም ተገልጿል።

Related Articles

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Back to top button