EthiopiaPolitics

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ የጋምቤላ ክልል አዲሱ አመራር

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ የጋምቤላ ክልል አዲሱ አመራር

 የህዝቡን ችግር ሊፈታ ይገባል አሉ፡፡

አርትስ 16/02/2011

የጋምቤላ ህዝቦች አንድነት ለዲሞክራሲያዊ  ንቅናቄ የማዕከላዊ ኮሚቴ በአዲስ አበባ እያካሄደ ባለው ግምገማ ፤የፓርቲው ሊቀመንበር እና የክልሉ መንግስት ፕሬዚዳንት የሆኑነት አቶ ጋትሉዋክ ቱት እናምክትላቸው አቶ ሰናይ አኩዎር ከኃላፊነታቸው ለቀው አቶ ኦሙድ ኡጁሉ የፓርቲው ሊቀመንበር አቶ አኙአያ ጃከን ደግሞ ምክትል ሊቀመንበር መሆናቸው ትናንት ተነግሯል፡፡

በግምገማው ላይ የተገኙት ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ የክልሉ ህዝብ ልማት የተጠማ በመሆኑ አዲሱ አመራር ጊዜውን በግል አጀንዳዎችና ሽኩቻ ከማጥፋ ይልቅ ራሱን ከጎሰኝነትና ከጥላቻበማጽዳት የክልሉን አመራር በማጠናከር የህዝቡን ችግር ሊፈታ እንደሚገባ መናገራቸዉን  የጠ/ሚኒስትር ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ፍፁም አረጋ አስታውቀዋል፡፡

ክልሉ በርካታ ሙያተኞች በየዩኒቨርሲቲው፣ በፌዴራል፣ በክልሉም ሆነ በዳያስፖራ የሚገኙ በመሆኑ እነዚህን በማፈላለግ በየደረጃው ክልሉን ለማጠናከር ቅድሚያ ሰጥቶ ሊንቀሳቀስ እንደሚገባም አሳስበዋልብለዋል፡፡

ከኃላፊነት የተነሱት አመራሮችም በድርጊታቸው ተጸጽተው ይቅርታ መጠየቃቸው እና ህዝቡን ለመካስ በተመደቡበት የስራ መስክ ለመሰማራት መወሰናቸው መልካም መሆኑ ተጠቁሟል፡፡

Related Articles

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Back to top button