Africa

የአፍሪካና የቻይና ግንኙነት ከፍተኛ ደረጃ ላይ ደርሷል ተባለ፡፡

ሮይተርስ እንዘገበው በቻይናና በአፍሪካ መካከል ያለው የንግድ ልውውጥ መጠን እስካለፈው ዓመት ድረስ 170 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር ደርሷል፡፡

በመጭው መስከረም ወር ላይ  የቻይና አፍሪካ የትብብር ፎረም  ቻይና ውስጥ ይካዳል፡፡

ፎረሙም በቻይናና በአፍሪካ መካከል ያለውን ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ግንኙነት የበለጠ ለማጠናከር ትልቅ ሚና ይኖረዋል ተብሏል፡፡

ቻይና ለአፍሪካ ሀገራት ለአቅም ግንባታ የሚውል 10 ቢሊዮን ዶላር የድጋፍ ገንዘብ መድባለች፡፡ ገንዘቡ  ለመሰረተ ልማት ግንባታ፣ ለሀይል ማመንጫ፣ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ ለታገዘ የግብርና ስራ ማስፋፊያ እንደሚውልም ታውቋል፡፡

Related Articles

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Back to top button