Africa

በአልጀሪያ ውሀን ብቻ የሚጠብቅ የፖሊስ ሀይል መቋቋም አለበት እየተባለ ነው፡፡

የሀገሪቱ መንግስት ሰሞኑን ውሀን በመበከል የህዝቡን ጤና አደጋ ላይ ጥለዋል ያላቸውን በርካታ ሰዎች ይዞ አስሯል፡፡

ግብጽ ውስጥ የሚታተመው ሾሩክ ጋዜጣ እንደዘገበው የተበከለ ውሀን አትክልት ለማጠጣት የተጠቀሙ እንዲሁም በውሀ ውስጥ ጤናን የሚጎዳ ውሁድ ጨምረዋል የተባሉ 1 ሺህ 744 ሰዎች በፖሊስ ቁጥጥር ስር ውለዋል፡፡

ከታሰሩት መካከል አብዛኛዎቹ በግብርና ስራ ላይ የተሰማሩ ሲሆኑ የታሰሩትም ከፍሳሽ ማስወገጃ በተለቀቀ ውሀ አትክልቶቻቸውን ሲያጠጡ በመገኘታቸው ነው፡፡

በአልጀሪያ ብዙ ሰዎች በኮሌራና ሌሎች ከውሀ ጋር ግንኙነት ባላቸው ህመሞች እየተያዙ ነው፡፡ በዚህም የተነሳ የአልጀሪያ የአካባቢ ደህንነት ጥበቃና የውሃ ሀብት ባለስልጣን መስሪያ ቤት ውሀን ብቻ የሚጠብቁ ፖሊሶች መኖር አለባቸው እያለ ነው ፡፡

አርትስ 25/12/2010

Related Articles

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Back to top button