Africa

ሮበረት ኪጉላኒ ለተሻለች ዩጋንዳ እንታገል ሲል ለደጋፊዎቹ ጥሪ አቀረበ ፡፡

አርትስ 9/1/2011
በቅጽል ስሙ ቦቢ ዋይን እየተባለ የሚጠራው ፖለቲከኛ ለህክምና ወደ አሜሪካ ከተጓዘበት ነገ ወደ ሀገሩ እንደሚመለስ አስታውቋል፡፡
አፍሪካ ኒውስ እንደዘገበው ዘ ፒፕል ፓወር የተባለው ንቅናቄ መሪ የሆነው ቦቢ ዋይን የሙሴቬኒ መንግስት ከወጣቶች ጋር እንዴት ተስማምቶ መስራት እንዳለበት ስለማያውቅ በጣም ይፈራናል ብሏል፡፡
ታዛቢዎች እንደሚሉት ዩዌሪ ሙሲቪኒ ለመጀመሪያ ጊዜ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ስብሰባን አልሳተፍም ማለታቸው ከፖለቲከኛው ወደ ሀገር ቤት መመለስ ጋር ተያይዞ ስጋት ገብቷቸው ነው ይላሉ፡፡
ሙሴቬኒ ግን እዛ ሄጀ የ15 ደቂቃ ንግግር አድርጌ ከምመለስ በሀገሬ በርካታ ስራዎችን ማከናወንን እመርጣለሁ የሚል መልስ ነው የሰጡት፡፡

Related Articles

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Back to top button