EthiopiaPoliticsSocial

በአዲስ አበባ እውቅና የተሰጠው ሰልፍ የለም

አርትስ 09/01/2011

በአዲስ አበባ መስከረም 10ቀን እውቅና የተሰጠው ሰልፍ አለመኖሩን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ፡፡

በከተማው ሕገ ወጥ ሰልፍ የሚደረግ ከሆነ በሕግ አግባብ እርምጃ እንደሚወሰድም ኮሚሽኑ ገልጿል፡፡

አንዳንድ ግለሰቦች ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ መሟለት ያለባቸውን መስፈርቶች ማለትም የሰልፉ አስተባባሪዎች ማንነትና አድራሻ፣ እንዲሁም ሰልፉ ላይ የሚገኝ የሰው ብዛት ሳያሳውቁ መስከረም 10 ቀን 2011 ዓ.ም በአዲስ አበባ ሰልፍ ለማድረግ መዘጋጀታቸውን ኮሚሽኑ አስታውቋል፡፡

ለህብረተሰቡ ሰላምና ደህንነት ሲባል አብዛኛው የጸጥታ ኃይል በሌላ የጸጥታ ስራ ላይ በተሰማረበት በአሁኑ ወቅት ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ ምቹ ሁኔታ አለመኖሩን ኮሚሽኑ አስታውቆ፣ ነገ መስከረም 10 ቀን 2011 ዓ.ም ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ መሟለት ያለባቸውን መስፈርቶች ሳያሟሉ ሰልፍ ለማድረግ የተዘጋጁ አካላት ከሕገ ወጥ ድርጊታቸው ሊታቀቡ እንደሚገባና ይህንን ማሳሰቢያ ተላልፈው በሚወጡ አካላት ላይ ኮሚሽኑ በሕግ አግባብ እርምጃ ለመውሰድ እንሚገደድ አስታውቋል፡፡
ኢ ቢ ሲ

Related Articles

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Back to top button