አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 1፣ 2013 ለ39 ዓመታት ያህል ራሱን ስቶ የቆየው የቀድሞ የፈረንሳይ እግር ኳስ ተጫዋች አረፈ፡፡ ለ39 ዓመታት ያህል ራሱን ስቶ የቆየው የቀድሞ የፈረንሳይ እግር ኳስ ተጫዋች ዣን-ፒር አዳምስ ህይወቱ አለፈ። በህክምና ስህተት የተነሳ ራሱን ስቶ ለ39 ዓመታት የቆየው የተከላካይ መስመር ተጫዋቹ ዣን-ፒር አዳምስ ለፓሪስ ሴይንት ጀርማይን ተጫውቶ አሳልፏል።
እ.አ.አ በ1982 ላጋጠመው የጉልበት ጉዳት ቀዶ ህክምና ለማድረግ ባለበት ወቅት የወሰደው ማደንዘዣ በአዕምሮው ላይ ባደረሰበት ጉዳት የተነሳ ራሱን ስቶ እንዲቆይ አድርጎታል። ሲ ኤን ኤን እንደዘገበው በ73 ዓመቱ ያረፈው አዳምስ በኮማ ውስጥ በቆየበት ጊዜ ውስጥ የባለቤቱ በርናዴት እንክብካቤ አልተለየውም ነበር ፡፡