EthiopiaPoliticsRegions

ኢህአዴግ አጋር ፖርቲዎችን ወደ ፓርቲነት ለማምጣት ጥናቱ እንዲጠናቀቅና ድርጅቱ የሁሉም እንዲሆን ይሰራል አሉ የድርጅቱ ሊቀመንበር እና ጠቅላይ ሚንስትር ዶ/ር አብይ አህመድ

አርትስ 23/01/2011
በ11ኛው የኢህአዴግ ድርጅታዊ ጉባዔ የመክፈቻ ስነ-ስርዓት ላይ ኢህአዴግ በ10ኛው ጉባዔ ከተወሰኑ ውሳኔዎች መካከል የድርጅቱን አጋር ፓርቲዎች ወደ ፓርቲነት ለማምጣት ጥናት እንዲደረግ የሚለው ቢገኝበትም አገሪቱ ወስጥ በነበረው ችግር ምክንያት ለዚህ ጉባዔ አለመቅረቡን የተናገሩት ጠ/ሚኒስትሩ ተጠንቶ እንደሚወሰን ተናግረዋል። አጋር ፓርቲዎችም በድጋፍ ንግግራቸው ጠቅሰውታል።
ዛሬ በሀዋሳ ከተማ የተጀመረው 11ኛው የኢህአዴግ ድርጅታዊ ጉባዔ የመክፈቻ ስነ-ስርዓት የድርጅቱ ህገ ደንብ በሚያዘው መሰረት ከ2ዓመት ስከ 2ዓመት ተኩል መካሄድ ያለበት ሲሆን ባለፈው መጋቢት ላይ መተላለፉ ይታወሳል።
ድርጅቱ ለ20አገራት የፖለቲካ ተወካዮች ጥሪ አቅርቦ የዘጠኝ አገራት ተወካዮች ተገኝተው ንግግር አድርገዋል።

Related Articles

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Back to top button