EthiopiaPoliticsRegionsSocial

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ ጎንደር ከተማ ገቡ

አርትስ 29/02/2011
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ ጎንደር የገቡት በነገው እለት በአማራ ክልል ጉብኝት ለማድረግ ጎንደር የሚገቡትን የኤርትራውን ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂን ለመቀበል ነው።
የኤርትራው ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ከነገ ጀምሮ በጎንደር እና ባህር ዳር ከተሞች ጉብኝት ያደርጋሉ።
ፕሬዚዳንት ኢሳያስ በነገው እለት ጎንደር ከተማ የሚገቡ ሲሆን፥ በቆይታቸውም በጎንደር እና አካባቢው የሚገኙ ታሪካዊ ቦታዎችን እና የልማት ስራዎችን እንደሚጎበኙ ይጠበቃል።
የፕሬዚዳንቱ ጉብኝት በሃገር ደረጃ የተጀመረውን ግንኙነት እንደሚያጠናክረው ታምኖበታል።
በጎንደር ከተማ በርካታ ኤርትራውያን በተለያየ ስራ ተሰማርተው ይገኛሉ።
ከዚህ ቀደም በአማራ ክልል አፈ ጉባኤ ወይዘሮ ወርቅሰሙ ማሞ የተመራ የልዑካን ቡድን በአስመራ ጉብኝት ማድረጉ የሚታወስ ነው።
ኤፍ ቢ ሲ

Related Articles

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Back to top button