EthiopiaLegal

ኢትዮጵያ የጦር መሳሪያ አጠቃቀም አዋጅ አፀደቀች፡፡

ኢትዮጵያ የጦር መሳሪያ አጠቃቀም አዋጅ አፀደቀች፡፡

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባካሄደው 33ኛ መደበኛ ስብሰባው የጦር መሳሪያ  አስተዳደር አዋጅ አፅድቋል፡፡

የረቂቅ አዋጁን አስፈላጊነት አስመልክቶ ማብራሪያ የሰጡት የመንግስት ረዳት ተጠሪ ሚኒስትር ዴኤታ  መስፍን ቸርነት የአገርና የህዝብን  ፀጥታ እና ሰላም ለማስጠበቅ ያለመ ነው ብለዋል፡፡

ግለሰቦች የታጠቋቸውን መሳሪዎች የሕብረተሰቡን ደህንነት በማስጠበቅ ተግባር ላይ እንዲያውሉ እንዲሁም ህገ-ወጥ የጦር መሳሪዎች ዝውውርን ለመቆጣጠር እንደሚያስችልም አብራርተዋል፡፡

በውይይቱ ወቅት የጦር መሳሪያ ፈቃድ የሚሰጣቸው አካላት መስፈርት በጣም ቀላል በመሆኑ ማንኛውም አካል ዝም ብሎ መሳሪያ እንዲታጠቅ በር አይከፍትም ወይ የሚል ጥያቄ ተነስቶም ማብራሪያ ተሰጥቶበታል፡፡

መረጃው  የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ነው፡፡

Related Articles

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Back to top button