Uncategorized

ባለፉት አምስት ወራቶች ከኢንዱስትሪ ፓርኮች 55 ሚሊዮን ዶላር ተገኘ

በኢትዮጵያ ተገንብተው ወደ ስራ ከገቡት የኢንዱስትሪ ፓርኮች ውስጥ ምርቶችን ወደ ውጭ በመላክ በአምስት ወር ውስጥ 55 ሚልዮን ዶላር ገቢ መገኘቱን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ገልጽዋል፡፡

የኮሚሽኑ የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር አቶ መኮንን ሃይሉ ለኢቢሲ እንደገለጹት የመቐለ፣ ቦሌ ለሚ ፣ኢስተርን ኢንዱስትሪ፣ ጆርጅ ሹ ፣ ኮምቦልቻ፣ ሃዋሳ ፣ ዩጃን ፣ ቬሎሲቲ እና የአዳማ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ያመረቱትን ምርት ወደ ውጭ መላክ ጀምረዋል፡፡

የኢንዱስትሪ ፓርኮቹ ለሃገሪቱ የውጭ ምንዛሬ ከማመንጨታቸውም በላይ በሺዎች ለሚቆጠሩ ዜጎች የስራ አድል ፈጥረዋል፡፡

በኢንዱስትሪ ፓርኮቹ የአንድ መስኮት ማዕከል አገልግሎት በመጀመሩ የባለሃብቱን ግዜ እና ገንዘብ መቆጠብ መቻሉን አቶ መኮንን አብራርተዋል፡፡

Related Articles

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Back to top button