EthiopiaPolitics

ጠ/ሚር አብይ አሕመድ በሰራዊቱ እኮራለሁ አሉ።

ጠ/ሚር አብይ አሕመድ በሰራዊቱ እኮራለሁ አሉ።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ኩራታቸዉን የገለጹት የ7ኛው የኢፌዲሪ ሀገር መከላከያ ሰራዊት ቀን ክብረ በዓል ላይ ባደረጉት ንግግር ነዉ፡፡

ጠ/ሚሩ በጦር ኃይሉ ውስጥ ግልጽነትና ሌሎች ክፍተቶችን ለመሙላት የተከናወኑ ዋና ዋና ለውጦችን በማንሳት የተመዝገበውንም ከፍተኛ ለውጥ አበረታች መሆኑን ገልጸዋል።

በዋናነትም ቁልፍ የሆነው የለውጡ መለያም ከፖለቲካ ወገንተኝነት የፀዳ ሙያዊ ብቃት ያለው ሰራዊት መገንባት ነው።

ዶክተር አብይ  መከላከያ ሰራዊቱን ከማዘመንና በሞያ ከማብቃት ጎን ለጎንም የኢትዮጵያ ወጣቶች የጦር ሰራዊቱን ዘመናዊ ተቋማት ግንባታና የቴክኖሎጂ ልህቀት እርምጃ እንዲያግዙ ጥሪ አቅርበዋል።

Related Articles

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Back to top button