SportSports

ዛሬ ምሽት በቶተንሃም እና አያክስ መካከል የቻምፒዮንስ ሊግ የግማሽ ፍፃሜ ጨዋታ ይደረጋል

የአውሮፓ ቻምፒዮንስ ሊግ የግማሽ ፍፃሜ የመጀመሪያ ዙር ጨዋታዎች ዛሬ እና ነገ ይከናወናሉ፡፡

የእንግሊዙ ቶተንሃም ሆተስፐር በአዲሱ ስታዲየም ዛሬ ምሽት 4፡00 ላይ የኔዘርላንድሱን አያክስ አምስተርዳም የሚገጥም ይሆናል፡፡

በአሰልጣኝ ማውሪሲዮ ፖቼቲኖ እየተመሩ በቻምፒዮንስ ሊጉ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ የግማሽ ፍፃሜ ተሳትፏቸውን እያደረጉ የሚገኙት ስፐርሶች ፤ በኢሪክ ቴን ሃግ ከሚመራው የበርካታ ወጣቶች ስብስብ እና ታላላቅ ቡድኖችን ጭምር ከውድድር እያሰናበተ እዚህ ደረጃ ላይ ይገኛል፡፡ ዛሬ ደግሞ ባለተራው የእንግሊዙ ቡድን ይሆን የሚለው ይጠበቃል፡፡

ስፐርሶች የጎል አዳኛቸውን ሃሪ ኬን ግልጋሎት በጉዳት ምክንያት በምሽቱ የማያገኙ ሲሆን ቡድኑ እዚህ ደረጃ ላይ እንዲደርስ ቁልፍ ሚና የነበረው ደቡብ ኮሪያዊው ሶን ሂንግ ሚን በቅጣት ምክንያት በጨዋታው የማይኖር ይሆናል፡፡ አማካዩ ሙሳ ሲሶኮ ልምምድ ጀምሯል፡፡   

በሆላንድ ኢርዲቪዚዬው ፒ.ኤስ.ቪን በግብ ክፍያ በመብለጥ ቀዳሚ ደረጃ ላይ የሚገኘው አያክስ ከ1996/97 በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ የፍፃሜ ተፋላሚ ለመሆን እያለመ ወደ ለንደን ተጉዟል፡፡

ነገ ምሽት ሌላኛው ተጠባቂ ግጥሚያ በባርሴሎና እና ሊቨርፑል መካከል ኑ ካምፕ ላይ ይደረጋል፡፡

Related Articles

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Back to top button