EthiopiaSocial

ጠ/ሚር አቢይ አሕመድ የጃፓን  የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ታሮ ካኖን ተቀብለው አነጋገሩ::

ጠ/ሚር ዐቢይ አሕመድ የጃፓን  የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ታሮ ካኖን ተቀብለው አነጋገሩ::

ሁለቱ ወገኖች በሁለትዮሽ፣ በቀጣናዊና ዓለም አቀፍ ጉዳዮች ዙሪያ መክረዋል::

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ታሮ ኮኖ ኢትዮጵያ እያካሄደች ያሉትን ማሻሻያዎችና በቀጣናው ያላትን የሰላም አስተዋጽዖ በመግለጽ ጠ/ሚር ዐቢይ አሕመድ ጃፓንን እንዲጎበኙ የጠ/ሚር ሽንዞ አቤን ግብዣ አቅርበዋል::

ጠ/ሚር ዐቢይ አሕመድ በበኩላቸው ጃፓን የኢትዮጵያ የልማት ተባባሪ መሆኗን አንሥተው በሰው ሀብት ዐቅም ግንባታ፣ በንግድና በኢንቨስትመንት ዘርፎች ቀጣይ ትብብር እንዲኖር ያላቸውን ፍላጎት ገልጸዋል::

Related Articles

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Back to top button