EthiopiaSportSports

48ኛው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ዛሬ ይጀመራል

ከ1963 ጀምሮ በየዓመቱ ሲካሄድ የነበረው ይህ ውድድር ዘንድሮ ለ48ኛ ጊዜ በአዲስ አበባ ስታዲየም ከሚያዚያ 29- ግንቦት 4/2011 ዓ/ም በ36 ክለቦችና ተቋማት መካከል ሲደረግ በአጠቃላይ 1376 አትሌቶች ይሳተፉበታል ተብሏል፡፡

የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ሁሉንም የአትሌቲክስ የውድድር ተግባራት በመካተት የሚካሄድ ይሆናል፡፡  

የውድድሩ ዓላማ በአገር ውስጥ የውድድር ዕድል መፍጠር ፤ በክልሎች፣ ከተማ አስተዳደሮችና ክለቦች እንዲሁም ተቋማት መካከል የአትሌቲክስ ፉክክር መፍጠር፣ ለብሔራዊ ቡድን አትሌቶች ለመምረጥ እና ለዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ሚኒማ ሊያሟሉ የሚችሉ አትሌቶችን በዕጩነት ለመምረጥ የሚል ነው፡፡

የውድድሩ አሸናፊ ለሚሆኑ አትሌቶች፣ ከአንዴ በላይ የወርቅ ሜዳሊያ ለሚያስመዘግቡ እና በቡድን ውጤት ለሚያስመዝግቡ አትሌቶች አንዲሁም ክብረወሰን ለሚያሻሽሉ አትሌቶች የገንዘብ ሽልማት ይኖራል ተብሏል፡፡

ከ2.1 ሚሊየን ብር በላይ በጀት የተያዘለት ይህ ሻምፒዮና አስፈላጊው ቅድመ ዝግጅት እንደተደረገ ተገልጧል፡፡   

Related Articles

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Back to top button