Uncategorized

የአሜሪካ ኮንግረስ አዲስ ታሪክ አስመዝግቧል፡፡ ምክር ቤቱ የመጀመሪያዋን ሙስሊም ሴት ተወካይ በማስመረጡ ነው አዲስ ታሪክ ተብሎ የተመዘገበለት፡፡

የአሜሪካ ኮንግረስ አዲስ ታሪክ አስመዝግቧል፡፡
ምክር ቤቱ የመጀመሪያዋን ሙስሊም ሴት ተወካይ በማስመረጡ ነው አዲስ ታሪክ ተብሎ የተመዘገበለት፡፡
አልጀዚራ እንደዘገበው ረሽዳ ጣሊብ የተባሉት ሴትም የዚህ አዲስ ታሪክ ባለቤት ለመሆን በቅተዋል፡፡ ጣሊብ ለምክር ቤት ወንበር ተወዳድረው አሸናፊ ለመሆን የበቁት በሚሽጋን ግዛት ነው ፡፡
የ42 ዓመቷ ወይዘሮ የዴሞክራቲክ ፓርቲ ተወካይ ሲሆኑ ተፎካካሪቸው ሆነው የቀረቡትን ብሬዳ ንጆንሰንን 33.6 በ28.5 በሆነ የድምጽ ልዩነት ነው ያሸነፏቸው ተብሏል፡፡
ጣሊብ ምርጫውን ካሸነፉ በኋላ ባደረጉት ንግግር ይህን ይሆናል ተብሎ የማይታመን ታሪክ ለሰራችሁ ደጋፊዎቸ በሙሉ ልባዊ ምስጋናዬን አቀርባለሁ ብለዋል፡፡

Related Articles

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Back to top button