አዲስ አበባ፣ ነሃሴ 11፣2013 በኢትዮጵያ ባለፉት 24 ሰዓታት 11 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ ምክንያት ህይወታቸው አለፈ፡፡ የጤና ሚኒስቴር በ24 ሰዓቱ የኮቪድ-19 ሪፖርት መረጃው ላይ እንዳስታወቀው ፤ በቫይረሱ ምክንያት 11 ሰዎች ህይወታቸው አልፏል፡፡ እስካሁንም በሀገሪቱ በኮሮና ምክንያት ህይወታቸውን ያጡ ሰዎች ቁጥርም 4 ሺህ 4 መቶ 89 ደርሷል፡፡
በ24 ሰዓታት ዉስጥ 5ሺህ 1 መቶ 73 ሰዎች ላብራቶሪ ምርመራ አድርገዉ 6 መቶ 88 ሰዎች ቫይረሱ ተገኝቶባቸዋል፡፡ በአጠቃለይ ቫይረሱ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር 2 መቶ 89 ሺህ 9 መቶ 62 ደርሷል፡፡ በጽኑ የታመሙ ሰዎች 434 ሲሆኑ ፤ በ24 ሰዓታት ውስጥ ከበሽታው ያገገሙ ሰዎች ደግሞ 218
ናቸዉ፡፡
አጠቃላይ ከቫይረሱ ያገገሙ ሰዎች ቁጥር ደግሞ 2 መቶ 65 ሺህ 5 መቶ 89 መሆኑን ከሚኒስቴሩ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡ የኮቪድ-19 ክትባት የተከተቡ ሰዎች ደግሞ 2 ሚሊዮን 3መቶ 14 ሺህ 394 ደርሷል፡፡