loading
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው አስቸኳይ ስብሰባ በሀገሪቱ ተጥሎ የቆየውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አነሳ፡፡

አዲስ አበባ፣ የካቲት 8፣ 2014 የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው አስቸኳይ ስብሰባ በሀገሪቱ ተጥሎ የቆየውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አነሳ፡፡ ምክር ቤቱ በስብሰባው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ እንዲነሳ በቀረበው የውሳኔ ሃሳብ ላይ ከተወያየ በኋላ በ63 ተቃውሞ በ21 ተአቅቦ በአብላጫ ድምጽ እንዲነሳ ወስኗል፡፡ ይህን ውሳኔ ተከትሎ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መርማሪ ቦርድ ከአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አፈጻጸም ጋር ተያይዞ […]

በክልሉ ሰላምን ለማደፍረስ በሚንቀሳቀሱ ኃይሎች ላይ ሕጋዊ እርምጃ እንደሚወስድ የሶማሌ ክልል አስታወቀ

በክልሉ ሰላምን ለማደፍረስ በሚንቀሳቀሱ ኃይሎች ላይ ሕጋዊ እርምጃ እንደሚወስድ የሶማሌ ክልል አስታወቀ፡፤ የሶማሌ ክልል መንግሥት ከሰላም ወዳዱ ህዝብ ጋር በመሆን የክልሉን ሰላምን ለማደፍረስ የሚንቀሳቀሱ ኃይሎችን እንደማይታገስና አስፈላጊውን ህጋዊ እርምጃ እንደሚወስድ ማስታወቁንየክልሉ ብዙኃን መገናኛ ድርጅት ዘግቧል። በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች በክልሉ ረብሻ፣ አለመረጋጋትና መንግስታዊ የኃላፊነት ቦታዎችን በኃይል ለመያዝ የተደረገ ሙከራ እንዳለ ተደርጎ የሚሰራጨው መረጃ ከእውነት የራቀ መሆኑንም […]

ህብረተሰቡ ሁለተኛውን ዙር የኮቪድ 19 መከላከያ ክትባት ወደ ክትባት መስጫ ጣቢያዎች በመቅረብ እንዲከተብ ጥሪ ቀረበ

የሁለተኛዉ ዙር የኮቪድ 19 መከላከያ ክትባት ዘመቻ እድሚያቸው 12 አመትና ከዚያ በላይ ለሆኑ ሁሉ በመንግስት ጤና ተቋማትና በጊዚያዊ ክትባት መስጫ ጣቢያዎች ከየካቲት 7 እስከ 16/2014 ዓ.ም መስጠት ተጀምሯል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጤና ቢሮ ሃላፊ ዶር ዮሃንስ ጫላ በሰጡት መግለጫ እንዳሳዎቁት፤እስካሁን ሰባት ሺህ 426 በላይ የሚሆኑ ሰዎች በወረርሽኙ ህይወታቸው አልፏል። ክትባቱን ተደራሽ ከማድረግ አንጻርም፤ እስካሁን […]

የሕወሓት ቡድን በአማራ ክልል ከተሞች አሰቃቂ ግፍና ወንጀሎችን መፈፀሙን አመንስቲ ኢንተርናሽናል ይፋ አደረገ፡፡

አዲስ አበባ፣ የካቲት 9፣ 2014 የሕወሓት ቡድን በአማራ ክልል ከተሞች አሰቃቂ ግፍና ወንጀሎችን መፈፀሙን አመንስቲ ኢንተርናሽናል ይፋ አደረገ፡፡ተቋሙ ዛሬ ባወጣው ሪፖርቱ የቡድኑ አባላት በአማራ ክልል ወረራ በፈጸመባቸው አካባቢዎች ሆን ብለው በርካታ ንጹሃንን መግደላቸውን፣ ሴቶችን በቡድን መድፈራቸውን እንዲሁም ከፍተኛ የግልና የመንግስትን ሃብት መዝረፋቸውን ተናግሯል፡፡ በተለይ ቆቦ እና ጭና በተባሉ ሁለት አካባቢዎች በነሃሴ መጨረሻና መስከረም መባቻ ላይ […]

የሆንዱራስ የቀድሞ ፕሬዚዳንት በአደንዛዥ ዕፅ ወንጀል ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር ዋሉ።

አዲስ አበባ፣ የካቲት 9፣ 2014 የሆንዱራስ የቀድሞ ፕሬዚዳንት በአደንዛዥ ዕፅ ወንጀል ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር ዋሉ። አሜሪካ የቀድሞ ፕሬዚዳንት ሁዋን ኦርላንዶ ሄርናንዴዝ በአደንዛዥ ዕፅ አዘዋዋሪነት ክስ ተላልፈው እንዲሰጧት ጥያቄ ካቀረበች ከሰዓታት በኋላ ነው በቁጥጥር ስር እንዲውሉ በፍርድ ቤት የዕስር ትዕዛዝየወጣባቸው ተብሏል፡፡ የፍርድ ቤቱ ቃል አቀባይ ሜልቪን ዱአርቴ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ በቀድሞው ፕሬዚዳንት ሄርናንዴዝ ላይ የእስር ማዘዣ […]

በተጭበረበረ መንገድ ለተሸከርካሪው ሊብሬና ታርጋ ሊያወጣ ሲሞክር በቁጥጥር ስር የዋለው ተከሳሽ የእስራትና የገንዘብ ቅጣት ተወሰነበት፡፡

አዲስ አበባ፣ የካቲት 9፣ 2014 በተጭበረበረ መንገድ ለተሸከርካሪው ሊብሬና ታርጋ ሊያወጣ ሲሞክር በቁጥጥር ስር የዋለው ተከሳሽ የእስራትና የገንዘብ ቅጣት ተወሰነበት፡፡ ታደለ ንጉሴ የተባለው ተከሳሽ የሙስናን ለመከላከል የወጣውን አዋጅ እዲሁም የጉምሩክና የፌደራልታክስ አስተዳደር አዋጆችን በመተላለፍ ወንወጀሎች ነው ክስ የተመሰረተበት፡፡ ተከሳሹ በሌላ ግለሰብ ስም በጊዜያዊነት ለቱሪስት አገልግሎት ወደ ሃገር ውስጥ የገባ ተሸከርካሪ ቀረጥና ታክስ ተከፍሎበት የገባ በማስመሰል […]

አማርኛ ቋንቋን የአፍሪካ ኅብረት የስራ ቋንቋ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ተናገሩ፡፡

አዲስ አበባ፣ የካቲት 10፣ 2014 አማርኛ ቋንቋን የአፍሪካ ኅብረት የስራ ቋንቋ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ተናገሩ፡፡ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ በሰጡት መግለጫ፤ በመዲናችን የተካሄደው 35ኛው የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባኤ ስኬታማ እንደነበርም ገልጸዋል፡፡ ኅብረቱ የአፍሪካ የበሽታዎች መከላከል ተቋምን ማጠናከር በሚቻልባቸው ሁኔታዎች ላይ መወያየቱንም ተናግረዋል፡፡ የኮቪድ- 19 መፍትሄዎቸ፣ የሰላምና የጸጥታ ችግር፣ […]

በአዲስ አበባ በትናትናው እለት በተከሰተው የእሳት አደጋ የሁለት ሰዎች ሕይወት ማለፉ ተገለጸ፡፡

አዲስ አበባ፣ የካቲት 10፣ 2014 በአዲስ አበባ በትናትናው እለት በተከሰተው የእሳት አደጋ የሁለት ሰዎች ሕይወት ማለፉ ተገለጸ፡፡ አዲስ አበባ አደጋና ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን የህዝብ ግንኙነት ባለሙያ አቶ ንጋቱ ማሞ እንደተናገሩት ÷ በመዲናዋ በትናንትናው ዕለት ሁለት የእሳት አደጋዎች ደርሰዋል፡፡አንዱ የእሳት አደጋ ትናንት 11 ሰዓት ከ50 ላይ በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 5 በመኖሪያ ቤት ላይ […]

የጀጎል ግንብ ከንፅህና ጉድለት ጋር በተያያዘ ምክንያት ችግሮች እየገጠሙት እንደሆነ የክልሉ ቱሪዝም ቢሮ አስታወቀ፡፡

አዲስ አበባ፣ የካቲት 11፣ 2014 የጀጎል ግንብ ከንፅህና ጉድለት ጋር በተያያዘ ምክንያት ችግሮች እየገጠሙት እንደሆነ የክልሉ ቱሪዝም ቢሮ አስታወቀ፡፡ በአሁኑ ወቅትም በዓለም ቅርስነት የተመዘገበውን የጀጎል ግንብ ለጎብኚዎች ምቹ ለማድረግ ህብረተሰቡን ያሳተፈ የማስዋብ ስራ እየተካሄደ ነው ተብሏል፡፡ “ጀጎልን ጽዱ እና ውብ እናድርጋት”  በሚል መሪ ሀሳብ በጀጎል የሚገኙ አሚር ኑር እና አባድር ወረዳዎችን በማስተባበር እና የህዝብ ንቅናቄ […]

ከ90 ዓመታት በላይ ያስቆጠረው የኢትዮጵያ የቆዳ ኢንዱስትሪ እያስመዘገበ ያለው ውጤት አነስተኛ መሆኑ ተገለጸ።

አዲስ አበባ፣ የካቲት 11፣ 2014 ከ90 ዓመታት በላይ ያስቆጠረው የኢትዮጵያ የቆዳ ኢንዱስትሪ እያስመዘገበ ያለው ውጤት አነስተኛ መሆኑ ተገለጸ። ኢትዮጵያ በእንስሳት ሃብቷ ከአፍሪካ ቀዳሚ ብትሆንም ያላትን ሃብት በአግባቡ መጠቀም ባለመቻሏ ውጤታማ እንዳልሆነችና በርካታ የቆዳ ውጤቶችን ከውጭ እንደምታስገባ ተነግሯል፡፡ በተለይ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የኮቪድ-19 ወረርሽኝና ሌሎች ችግሮች ለኢንዱስትሪው የገበያ መቀዛቀዝ ምክንያት መሆኑን የኢትዮጵያ ቆዳ ኢንዱስትሪ ልማት ኢንስቲትዩት […]