loading
ኢትዮጵያ በግድቡ ዙሪያ ግልፅ መርህ አስቀምጣ እየተጓዘች ነው-ኢንጅኔር ስለሺ በቀለ

አዲስ አበባ ፣ ሃምሌ 6፣ 2013 ኢትዮጵያ በግድቡ ዙሪያ ግልፅ መርህ አስቀምጣ እየተጓዘች ነው-ኢንጅኔር ስለሺ በቀለ የውኃ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስትሩ ዶክተር ኢንጅነር ስለሺ በቀለ ለተባበሩት መንግሥታት ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ በታላቁ የህዳሴ ግድብ ዙሪያ ማብራርያ ሰጡ፡፡ ሚኒስትሩ ለዋና ጸሐፊው ግንባታው ስላለበት ሁኔታ፣ ስለሁለተኛ ዙር የውኃ ሙሌት እንዲሁም በአፍሪካ ህብረት አደራዳሪነት ስለሚካሄደው ድርድር ተገቢውን ማብራሪያ ሰጥተዋል ። […]

የአማራ ጠቅላይ ፍርድ ቤት በባለ ስልጣናት ግድያ በተጠረጠሩ ግለሰቦች ላይ የመከላከያ ምስክሮችን መስማት ጀመረ፡፡

አዲስ አበባ ፣ ሃምሌ 6፣ 2013   የአማራ ጠቅላይ ፍርድ ቤት በባለ ስልጣናት ግድያ በተጠረጠሩ ግለሰቦች ላይ የመከላከያ ምስክሮችን መስማት ጀመረ፡፡ ፍርድ ቤቱ በሰኔ 15 ቀን 2011 ዓ.ም. በአማራ ክልል ባለስልጣናት ግድያ እጃቸው አለበት በተባሉት በእነሻምበል መማር ጌትነት መዝገብ የተከሰሱ 32 ተከሳሾችን የመከላከያ ምስክሮች ነው ማዳመጥ የጀመረው፡፡ በዚሁ የክስ መዝገብ ጉዳያቸው ሲታይ ከነበሩት 55 ተከሳሾች […]

ግብፅ የሙስሊም ወንድማማቾች ህብረት አባላት ላይ የዕድሜ ልክ እስራ  ውሳኔ አስተላለፈች፡፡

አዲስ አበባ ፣ ሃምሌ 6፣ 2013 ግብፅ የሙስሊም ወንድማማቾች ህብረት አባላት ላይ የዕድሜ ልክ እስራ  ውሳኔ አስተላለፈች፡፡ የሀገሪቱ ከፍተኛ ይግባኝ ሰሚ ችሎት የፖሊስ አባላትን በመግደልና እስር ቤት ሰብረው እስረኞችን በማስመለጥ ወንጀል በተከሰሱ የህብረቱን መሪ ሞሐመድ ባዴን ጨምሮ በ10 ግለሰቦች ላይ ነው ወሳኔውን ያሳለፈው፡፡ ተከሳሾቹ እንደ አውሮፓያኑ አቆጣጠር በ2011 በግብፅ በተቀሰቀሰው አብዮት 20 ሺህ የሚሆኑ እስርኞችን እንዲያመልጡ […]

በኢራቅ በኮሮና ቫይረስ ማገገሚያ ማዕከል በተነሳ የእሳት አደጋ የበርካታ ሰዎች ህይዎት ማለፉ ተሰማ፡፡

አዲስ አበባ ፣ ሃምሌ 6፣ 2013 በኢራቅ በኮሮና ቫይረስ ማገገሚያ ማዕከል በተነሳ የእሳት አደጋ የበርካታ ሰዎች ህይዎት ማለፉ ተሰማ፡፡ በማገገሚያ ማዕከሉ በተቀሰቀሰው ቃጠሎ ከ64 በላይ ሰዎች ለህልፈት ሲዳረጉ 70 የሚሆኑት ደግሞ ቀላልና ከባድ ጉዳት እንደደረሰባቸው የሀገሪቱ ፖሊስ ይፋ አድርጓል፡፡ ፖሊስ የእሳት አደጋው መንስኤ በውል ባይታወቅም በሆስፒታሉ የሚገኝ ኦክስጂን መፈንዳት የአደጋው ሳይሆን እንዳልቀረ ነው የገለጸው፡፡ አደጋውም […]

የአማራ ክልል በህወሓት ላይ የተጀመረው “ሕግን የማስከበር” ትግል ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ አቀረበ::

አዲስ አበባ ፣ ሃምሌ 7፣ 2013  የአማራ ክልል በህወሓት ላይ የተጀመረው “ሕግን የማስከበር” ትግል ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ አቀረበ:: በትግራይ ክልል በህወሓት ላይ የተጀመረው ሕግን የማስከበር ትግል ተጠናክሮ እንዲቀጥል የኢትዮጵያ ሕዝብ አስፈላጊውን ርብርብ እንዲያደርግ የአማራ ክልል ጠየቀ፡፡ ክልሉ ትናንት ባወጣው መግለጫ “ትህነግ አገር ከማፍረስ እኩይ ተልዕኮው ሊታቀብ የሚችለው የአገራችንን ሉአላዊነትና የግዛት አንድነት በጽናትና በአላማ ቁርጠኝነት በጋራ […]

የቀጥታ በረራም ሆነ ከአውሮፕላን ላይ እርዳታ መጣል የሚለው ሀሳብ ተቀባይነት የላቸዉም::

አዲስ አበባ ፣ ሃምሌ 8፣ 2013 ለትግራይ ክልል የሰብዓዊ ድጋፍ በቀጥታ በረራም ሆነ የሀገር ሉዓላዊነትን በሚጥስ ሌላ ተግባር የሚደረግ እንቅስቃሴ አይፈቀድም ተባለ:: የብሔራዊ የአደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ኮሚሽነር ምትኩ ካሳ በተለይ ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደገለጹት፤ በዓለም ምግብ ፕሮግራምና ሌሎች ዓለም አቀፍ የእርዳታ ተቋማት በኩል ምግብና ምግብ ነክ ያልሆነ የእርዳታ አቅርቦቶች በተገቢው መንገድ ወደ መቀሌ እንዲያጓጓዙ […]

በትግራይ ኤርትራዊያን ስደተኞች ደህንነታቸው አደጋ ላይ መሆኑ ተገለፀ::

አዲስ አበባ ፣ ሃምሌ 8፣ 2013 በትግራይ ኤርትራዊያን ስደተኞች ደህንነታቸው አደጋ ላይ መሆኑ ተገለፀ:: አሸባሪው ህወሓት ስደተኞች በሰፈሩባቸው አካባቢዎች ጥቃቶች መክፈቱን የስደተኞችና ከስደት ተመላሾች ኤጀንሲ አስታወቀ፡፡ ኤጀንሲው ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ባለከው መግለጫ እንደገለጸው፤ ህወሓት የመንግስትን የተናጠል የተኩስ አቁም ውሳኔ ውድቅ አድርጎ ስደተኞች ላይ ጥቃት እየፈጸመ ነው። በዚህ የህወሓት ጥቃት ምክንያት በማይ-ዓይኒ እና በአዲ-ሐሩሽ መጠለያ ጣቢያዎች […]

የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ሁለተኛው ዙር የውሃ ሙሌት በስኬት ተጠናቀቀ::

አዲስ አበባ ፣ ሃምሌ 12፣ 2013 የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ሁለተኛው ዙር የውሃ ሙሌት በስኬት ተጠናቀቀ::ውሃው በግድቡ አናት ላይ መፍሰስ መጀመሩ ተነግሯል ዛሬ ሐምሌ 12 ቀን 2013 ዓም የሁለተኛውን አመት የህዳሴ ግድብ ሙሌት ተገባዶ ውሃው በግድቡ አናት ላይ መፈሰስ መጀመሩን የውሃ መስኖ እና ኢነርጂ ሚኒስትሩ አስታውቀዋል።ሚኒስትሩ ዶክተር ኢንጅነር ስለሺ በቀለ በትዊተር ገጻቸው ላይ ውሃው በግድቡ […]

ኢትዮጵያ በጽናት ትገሰግሳለች-ጠ/ሚ ዐቢይ::

አዲስ አበባ ፣ ሃምሌ 12፣ 2013  ጠ/ሚ ዐቢይ ለታላቁ ህዳሴ ግድብ 2ኛው ዙር የውሃ ሙሌት በስኬት መጠናቀቁን ተከትሎ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላለፉ:: ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጉዳዩን አስመልክተው በትዊተር ገፃቸው ላይ ባሰፈሩት መልዕክት ኢትዮጵያ በጽናት ትገሰግሳለች ብለዋል፡፡ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ አቶ ደመቀ መኮንን በማህበራዊ የትስስር ገጻቸው ላይ ÷የታላቁ ህዳሴ ግድብ ፕሮጀክት ሁለተኛ ዙር የውሃ ሙሌት መርሃግብር […]

በጣና ሀይቅ በተሰወረችው ጀልባ ህይወታቸው ያለፉ ሰዎች አስክሬን ተገኘ::

አዲስ አበባ ፣ ሃምሌ 12፣ 2013 በጣና ሀይቅ በተሰወረችው ጀልባ ህይወታቸው ያለፉ ሰዎች አስክሬን ተገኘ:: በጣና ሀይቅ በተሰወረችው ጀልባ ህይወታቸው ያለፈ የ7 ሰዎች አስክሬን ተገኘ በማእከላዊ ጎንደር ዞን ምስራቅ ደንቢያ ወረዳ በጣና ሀይቅ 13 ሰዎችን አሳፍራ በጉዞ ላይ እንዳለች በተሰወረችው አነስተኛ ጀልባ ህይወታቸው ያለፈ የሰባት ሰዎች አስክሬን መገኘቱን ፖሊስ አስታወቀ። የወረዳው ፖሊስ ፅህፈት ቤት ሃላፊ […]