loading
በጅቡቲ ወደብ በኩል ወደ ኢትዮጵያ በሽፋን የገባው ሁለት ኮንቴነር ህገወጥ የጦር መሳሪያ በቁጥጥር ስር ዋለ::

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 2፣ 2012 አለም አቀፍ የጦር መሳሪያ አዘዋዋሪ ቡድን በጅቡቲ ወደብ በኩል ወደ ኢትዮጵያ በሽፋን ያስገባው ሁለት ኮንቴነር ህገወጥ የጦር መሳሪያ በቁጥጥር ስር እንዲውል ማድረጉን የብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ባወጣው መግለጫ አስታውቋል። መነሻውን ከቱርክ ሜርሲን ወደብ ያደረገው ህገወጥ የጦር መሳሪያው፤ በጅቡቲ ወደብ በኩል ወደ ኢትዮጵያ በሽፋን ገብቶ በቁጥጥር ስር የዋለው፤ በወደቡ ለአምስት ወራት […]

የአፍሪካ ህብረት ሰንደቅ ዓላማ ከኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ ጋር አብሮ እንዲውለበለብ የሚደነግገው አዋጅ ለውጭ ግንኙነትና ሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ተመራ::

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 2፣ 2012 አምስተኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በአምስተኛ አመት የስራ ዘመኑ ባካሄደው 13ኛ መደበኛ ስብሰባው ነዉ  የአፍሪካ ህብረት ሰንደቅ ዓላማ ከአገራችን ብሔራዊ ሰንደቅ ዓላማ ጋር አብሮ እንዲውለበለብ የሚደነግገውን ረቂቅ አዋጅ ለውጭ ግንኙነትና ሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ  የመራው፡፡ምክር ቤቱ የአፍሪካ ህብረት ሰንደቅ ዓላማ፣ መዝሙር እና የአፍሪካ ቀንን በሚመለከት የቀረበውን ረቂቅ አዋጅ ለዝርዝር እይታ […]

ሶልቭ ኢት የተባለዉ የፕሮጀክት መተግበሪያ ሀሳብ ያላቸዉን ወጣቶች ለማበረታታትና ለወጣቶች እድልን ለማመቻቸት ያለመ መሆኑ ተገለፀ፡፡

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 2፣ 2012 በአንድ ሀገር የሰላም እጦት ሁነት  ሲበዛ ብዙ ምስቅልቅሎች ይፈጠራሉ፡፡ የአብዛኞቹ የሰላም እጦት  መነሻ ደግሞ ከወጣቶች  የስራ አጥነት ጋር ይያያዛል ፡፡የኢትዮጵያም ከዚህ የተለየ አይደለም ፡፡በኢትዮጵያም የስራ አጥነት ችግር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተባባሰ መጥቶ አሁን ላይ የተማረዉ ያልተማረዉም  ወጣት ስራ አጥ መሆኑ የተለመደ ሆኗል፡፡ታዲያ ችግሩን ለመቅረፍ  ጥረቶች ቢደረጉም ከችግሩ ስፋት አንጻር  ለወጣቶች […]

በመርካቶ ከ1ሺ በላይ ግብር ከፋዮች ላይ አስተዳደራዊ ቅጣት ተጣለ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 3፣ 2012 ቅጣቱ የተጣለዉ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ ባለፉት ሰባት ወራት በመርካቶ ባደረገው ቁጥጥር ነዉ፡፡ቅጣት የተጣለባቸዉ የሽያጭ መመዝገቢያ መሳሪያዎችን በአግባቡ ባልተጠቀሙና ያለደረሰኝ ግብይት ሲፈጽሙ በተገኙ አንድ ሺ 71 ግብር ከፋዮች ላይ ሲሆን፡ከ 40 ሚሊዮን ብር በላይ አስተዳደራዊ ቅጣት መጣሉን አስዉቋል። በቢሮው የህግ ተገዥነት ዘርፍ፤ የታክስ መረጃና የሽያጭ መመዝገቢያ አስተዳደር ዳይሬክተር […]

በሰሜን ጎንደር ደጋማ ወረዳዎች የበረሃ አንበጣ መንጋ እየተስፋፋ መሆኑ ተገለጸ፡፡

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 3፣ 2012 በሰሜን ጎንደር ዞን ደጋማ ወረዳዎች ማለትም በየዳ፣ ጠለምትና ጃናሞራ ወረዳዎች ባለፈ አድማሱን በማስፋት በወረዳዎች ስር በሚገኙ 32 ቀበሌዎች ላይ የአንበጣ መንጋው ተስፋፍቷል ተብሏል። የሰሜን ጎንደር ዞነ ግብርና መምሪያ የኤክስቴንሽን ቡድን መሪ አቶ ዋለ መርሻ ለአማራ ብዙሃን መገናኛ እንደገለጹት፡ መንጋው አሁን ላይ የሰብል ወቅት ባለመሆኑ ጉዳት ባያደርስም የመስኖ ሰብሎች ለይ ጥፋት […]

አውሮፓ ህብረት ከቻይና እና አሜሪካ ጋር በአፍሪካ የሚያፎካከረውን አዲስ ስትራቴጂ ይፋ አደረገ::

  አዲስ አበባ፣ መጋቢት 3፣ 2012 የአውሮፓ ህብረት በአፍሪካ ያለውን ግንኙነት በእጥፍ እንደሚጨምር የተነገረለትን አዲስ እና ሁሉን አቀፍ ስትራቴጂ ነው ይፋ ያደረገው፡፡ ህብረቱ ይፋ ያደረገው አዲስ ስትራቴጂ በአፍሪካ ንግድ እና ኢንቨስትመንት የቻይና ፣የአሜሪካንና የሩሲያን ድርሻ ለመጋራት የሚያስችል ነው ተብሏል፡፡ አፍሪካ ኒውስ እንደዘገበው አውሮፓ ከአፍሪካ ጋር ያለው የውጭ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንት 235 ቢሊየን ዩሮ ቢደርስም በቻይናና በአሜሪካ […]

የኮሮና ቫይረስ ቅድመ መከላከል ላይ ይበልጥ መስራት እንደሚያስፈልግ የህዝብ ተወካዮች ምክርቤት አባላት ተናገሩ፡፡

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 4፣ 2012 የኮሮና ቫይረስ ቅድመ መከላከል ላይ ይበልጥ መስራት እንደሚያስፈልግ የህዝብ ተወካዮች ምክርቤት አባላት ተናገሩ፡፡ ይህንን ያሉት ከምክርቤቱ 14ተኛ መደበኛ ስብሰባ ጎን ለጎን የጤና ሚኒስትርና  የህብረተሰቡ ጤና  እንስቲትዮት በሀገሪቱ ቫይረሱን በተመለከተ እየተሰሩ ያሉትን ስራዎች በአብራሩበት ወቅት ነዉ ፡፡ በሀገር አቀፍ ደረጃ በየብስ በአየርም 520 ሺ የሚሆኑ መንገደኞች ወደ ሀገር የገቡ ሲሆን 958ቱ […]

ልዩነትን በሰለጠነ መንገድ በመፍታት ለሀገር ሠላምና ዘላቂ ልማት መቆም እንደሚገባ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገለጹ፡፡

ልዩነትን በሰለጠነ መንገድ በመፍታት ለሀገር ሠላምና ዘላቂ ልማት መቆም እንደሚገባ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገለጹ፡፡ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር  አቶ ደመቀ መኮነን በባህር ዳር “የጋራ ራዕይና ግብ ለአማራ ሕዝብ ዘለቄታዊ አንድነትና ሁለንተናዊ ስኬት” በሚል መሪ ሐሳብ  በተካሄደዉ ጉባኤ ላይ አንደተናገሩት የታፈረች ሀገር መመሥረት የሚቻለው በትንንሽ አጀንዳዎች ላይ ጊዜን በማጥፋት ሳይሆን ትላልቅ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ትኩረት ሰጥቶ በመሥራት […]

ለህዳሴ ግድብ ግንባታ የቦንድ ሳምንት  በማዘጋጀት 500 ሚሊዮን ብር ለማግኘት ታቅዷል፡፡

ለህዳሴ ግድብ ግንባታ የቦንድ ሳምንት  በማዘጋጀት 500 ሚሊዮን ብር ለማግኘት ታቅዷል፡፡ የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ሕዝባዊ ተሳትፎ ማስተባበሪያ ጽሕፈት ቤት ከመጋቢት 15 ቀን 2012 ዓ.ም ጀምሮ በሚኖረው የቦንድ ሳምንት 500 ሚሊዮን ብር ለማግኘት መታቀዱን ገለጸ። ለግድቡ ግንባታ በሰባት ወራት ጊዜ ውስጥ 400 ሚሊዮን ብር ብቻ መሰብሰቡን ያስታወሰዉ የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ሕዝባዊ ተሳትፎ ማስተባበሪያ ጽሕፈት […]

የብልጽግና ፓርቲ የትግራይ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቱን በመቀለ ከተማ መክፈቱን አስታወቀ።

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 9፣ 2012የብልጽግና ፓርቲ የትግራይ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቱን በመቀለ ከተማ መክፈቱን አስታወቀ። የፓርቲው የሕዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ኃላፊ አቶ አወሉ አብዲ  በሰጡት መግለጫ እንደተናገሩት፤ ብልጽግና ፓርቲ አገራዊ ፓርቲ በመሆኑ በሁሉም ክልሎች ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቶቹን ከፍቶ እንደሚንቀሳቀስ ቃል በገባው መሰረት የትግራይ ክልል ቅርንጫፉን በመቀለ ከተማ ከፍቷል። የትግራይ ክልል የለውጡ አንድ አካል በመሆኑ የትግራይን […]