 
      
         ጥቂት ስለ ወ/ሮ ቢልለኔ ስዩም
ጥቂት ስለ ወ/ሮ ቢልለኔ ስዩም
አርትስ 26/02/2011
ትናንት የጠቅላይ ሚኒስትር ፅህፈት ቤት ፕረስ ሴክሬታሪ ሆና የተሾመችው  ቢልለኔ ስዩም  የተወለደችው አዲስ አበባ ነው፡፡ የእድገቷን የተወሰነ ጊዜ በዙምባብዌ ሀረሬ ያሳለፈች ሲሆን በተለያዩ ሀገራትትምህርቷን ተምራለች ።
በአለም አቀፍ ግንኙነት የመጀመሪያ ድግሪዋን ካናዳ ከሚገኘው ብሪቲሽ ኮሎምቢያ ዩንቨርሲቲ አግኝታለች ።
የሁለተኛ ድግሪ ትምህርትዋን  በጀንደርና ፒስቢዩልዲንግ ኮስታሪካ ከሚገኘው የተባበሩት መንግስታት ማንዴትድ ዩንቨርስቲ ተከታትላለች ።
ሌላ ሁለተኛ ድግሪ በፒስ ስተዲስ ኦስትሪያ ከሚገኘው ዩንቨርስቲ ኦፍ ኢንስብረክ አግኝታለች ።
ቢልለኔ በተለያዩ ደረጃዋች የአማካሪነትና አስተባባሪነት በሰው ሀይል ግንባታ ስራን ሰርታለች ከአነዚህም ውስጥ በአፍሪካ ህብረት እና ከእናት ባንክ ጋር የሰራቻቸው ስራዎች ተጠቃሽ ሲሆኑ ተመሳሳይስራንም በካናዳ ሰርታለች ። የተለያዩ ፕሮጀክቶችን በዋና አስተዳዳሪነት መርታለች ።
