loading
ዲያስፖራ ኖት?

ዲያስፖራ ኖት?

እንግዲያዉስ የኢትዮጵያ የዲያስፖራ ትረስት ፈንድ የባንክ ሂሳብ ቁጥር ይፋ ሆኗልና እንንገርዎ።

ይህም በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የኢትዮጵያ ዲያስፖራ ትረስት ፈንድ በሚል ስም ሲሆን ሂሳቡ የተከፈተዉ፤የሂሳብ ቁጥሩም 1000255726725 ነዉ፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ በውጭ ሃገራት የሚገኙ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን በየቀኑ ቢያንስ አንድ ዶላር ወደ ኢትዮጵያ በመላክ ለተለያዩ የልማት ስራዎች ድጋፍ እንዲያደርጉ ጠይቀው ነበር። ለዚህም ስራ እንዲዉል ነዉ የባንክ ሂሳብ ቁጥሩ የተከፈተዉ፡፡

ገንዘቡን ለማስገባትም በቅርቡ ድረ- ገጽ የሚከፈት ሲሆን እሱን በመጠቀም፥ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክን ስዊፍት አድራሻዎችን በመጠቀም ገንዘቦቹን ማስገባት ይቻላል ተብሏል፡፡

Write a Reply or Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *