loading
መንግስት ባወጣው የምህረት አዋጅ ተጠቃሚ ለመሆን ከታራሚዎች ምን ይጠበቃል?

መንግስት ባወጣው የምህረት አዋጅ ተጠቃሚ ለመሆን ከታራሚዎች ምን ይጠበቃል?
መንግስት ያወጣው የምህረት አዋጅ ከወጣበት ሐምሌ13ቀን 2010 ዓ.ም ጀምሮ ተፈጻሚ ይሆናል ተብሏል፡፡
የምህረት አሰጣጡ ለሚቀጥሉት 6 ወራት ስራ ላይ የሚውል ሲሆን፤ የምህረቱ ተጠቃሚ የሚሆኑ ታራሚዎች የተጠየቁበት ወንጀል እስከ ግንቦት 30 የተፈጸመ ከሆነ ብቻ ነዉ ተብሏል፡፡
የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ አቶ ብርሃኑ ፀጋዬ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ በእነዚህ 6 ወራት ውስጥ የምህረቱ ተጠቃሚ ለመሆን ታራሚዎች በአካል በመገኘት ፣ ሰው በመወከል ወይም በፖስታ እና ስልክ ለፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ የምህረት እና ይቅርታ ጽህፈት ቤት፣በክልል ፍትህ ቢሮዎች ሪፖርት ማድረግ እና መመዝገብ አልያም ወደ www.fag.gov.et ድረ-ገጽ በመግባት የሚጠየቁትን መረጃዎች በመሙላት መመዝገብ ይኖርባቸዋል ብለዋል፡፡
ምዝገባውን አለማድረግ ምህረቱን አለመቀበል ተደርጎ ስለሚወሰድ በአዋጁ ተጠቃሚ እንዳይሆኑ ያደርጋል ፡፡ምህረት የተደረገለት ታራሚም የማረጋገጫ ሰርተፊኬት እንደሚሰጠው ተነግሯል፡፡

Write a Reply or Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *