loading
እንግሊዝ የዚምባቡዌ ነገር አሳስቦኛል ብላለች፡፡

አሁንም በአፍሪካ ምድር በምርጫ ማግስት ሰው ይገደላል፡፡ በዚምባቡዌ የተካሄደው ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ውጤቱ ለሰው ህይወት መጥፋት ምክንያት ሆኗል፡፡
የፕሬዝዳንት ኤመርሰን ምናንጋግዋ ዋነኛ ተፎካካሪ ሆነው በምርጫው የቀረቡት ኔልሰን ቻሚሳ የዛኑ ፒ ኤፍ ፓርቲ አሸናፊ ሆኗል መባሉን ባለመቀበላቸው ደጋፊዎቻቸው ለተቃውሞ ሰልፍ አደባባይ ወጥተዋል፡፡
የምናንጋግዋ ወታደሮችም ሰልፈኞቹ ላይ ተኩሰዋል፡፡ እስካሁን 3 ሰዎች መገደላቸው ታወቋል፡፡ እንዲያውም አንዳንድ መገናኛ ብዙሀን ቁጥሩን አምስት ያደርሱታል፡፡
የኬንያው ደይሊ ኔሽን እንደዘገበው የቀድሞ ቅኝ ግዛቷ ጉዳይ እንዳሳሰባት የገለጸችው እንግሊዝ የሀገሪቱን ባለስልጣናት ነገር አብርዱ እያለች ነው፡፡

Write a Reply or Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *