loading
አዲስ ይፋ የሆነው የትምህርት ፍኖተ-ካርታ ትምህርት ሚኒስቴርን ሦስት ቦታ የሚያደራጅ ነው::

አዲስ ይፋ የሆነው የትምህርትና ስልጠና ፍኖተ-ካርታ ትምህርት ሚኒስቴርን በሦስት ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች የሚያደራጅ መሆኑ ተጠቆመ።
በትምህርት ዘርፍ አስተዳደር ላይ ማሻሻያ ያቀረቡት የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ ምክትል ፕሬዝዳንት ዶክተር ጄይሉ ዑመር እንዳሉት ፍኖተ-ካርታው ብዙ መዋቅራዊ ለውጦችን የያዘ በመሆኑ ትምህርት ሚኒስቴር በሦስት ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች እንዲደራጅ የሚያደርግ ነው።
በአዲስ መልክ የሚቋቋሙት ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች የከፍተኛ ትምህርትና ስልጠና ሚኒስቴር፣ አጠቃላይ የትምህርትና ስልጠና ሚኒስቴር እና የክህሎትና ሥራ ፈጠራ ሚኒስቴር ተብለው እንደሚዋቀሩ ገልጸዋል። ዶ/ር ጄይሉ እንዳሉት የተማሪዎች የዩኒቨርሲቲ ቆይታ ጊዜ ዝቅተኛው አራት ዓመት ሲሆን እንደ ምህንድስናና ህክምና የትምህርት ፕሮግራሞች ደግሞ ስድስት ዓመት እንዲሆኑ ሀሳብ ቀርቧል።
ኢቢሲ እንደዘገበዉ፡፡

Write a Reply or Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *