loading
በሚቀጥሉት ሁለት ሳምንታት የሰሞኑ ከባድ ዝናብ ይቀጥላል ተባለ፡፡

ይህንን ያለዉ የብሄራዊ ሜትሮሎጂ ኤጀንሲ ነዉ፡፡
የኤጀንሲዉ ዋና ዳይሬክተር አቶ ፈጠነ ተሾመ ዛሬ በሰጡት መግለጫ እንደተናገሩት፤ከሰሞኑ የዘነበዉ ከባድ ዝናብ ይቀጥላለ፤በተለይ በምእራብ አጋማሽ የሀገሪቱ ክፈሎች፤አልፎ አልፎ በጸሀይ ሀይል የሚታገዝ የዳመና ክምችቶች ጋር ተያይዞ ጎርፈና ከባድ ዝናብ ሊያጋጥም እንደሚችል ተናግረዋል፡፡
ከግድብና ከተፋሰስ ጋር የሚሰሩ ስራዎች በከፍተኛ ጥንቃቅና በተለየ ትኩረት መሰራት እንዳለባቸዉ አቶ ፈጠነ ተናግረዋል፡፡
ከዝናቡ ጋር ተያይዞ በሰዉ ህይወት በእንስሳትና በንብረት አደጋ እንዳይደረስ ከሚመለከታቸዉ ጋር በጋራ እየሰራን ነዉ ብለዋል፡፡

Write a Reply or Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *