loading
የግብጹ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሳሜህ ሽኩሪ ዛሬ ወደ አዲስ አበባ ይመጣሉ፡፡

ከውጭ ጉዳይ ሚንስቴር ቃል አቀባይ ጽህፈት ቤት ድረገፅ ያገኘነው መረጃ እንደጠቆመው የግብፅ ውጭ ጉዳይ ሚንስትር ሳሚህ ሹክሪ እና የደህንነት ሀላፊው አባስ ካሚል የሚመራው ከፍተኛ ልዑክ አዲስ አበባ ይገባሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡
የሃገሪቱ ከፍተኛ ልዑካንም ፕሬዝዳንት አብዱል ፈታህ አልሲሲ ለጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ የላኩትን መልእክት ይዘው እንደሚመጡ ተነግሯል፡፡
ልዑካኑ በአዲስ አበባ ቆይታቸው በመሰረተ ልማት ግንባታዎች ላይ በጋራ ለመስራት፣ በአፍሪካ ቀንድ ሰላምና ፀጥታን ማስፈን በሚቻልበት ሁኔታ ጋር ይወያያሉ ተብሏል፡፡

Write a Reply or Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *