loading
የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ከሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ጋር በመተባበር በድሮን ቴክኖሎጂ የታገዘ የጤና አገልግሎት ሙከራ ጀመረ

አርትስ 02/01/2011
መሰረታዊ የሆኑ መድሃኒቶች፣ የክትባት መድሃኒትና ደምን ለማጓጓዝ በጋራ እየሰራን ሲሆን ዛሬ ሙከራ አድርገናል ብለዋል ሚኒስትሩ ዶ/ር አሚር አማን፡፡
ድሮንውኑ በማንኛውም የአየር ፀባይ የሚሰራ ፣ እስከ 5ኪ.ግ ክብደት መሸከም የሚችል፣ በደርሶ መልስ 300 ኪ.ሜ መሸፈን የሚችልና እስከ 5000 ሜትር ከፍታ የሚነሳ ሲሆን ለዚህም የሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ዶ/ር ኢንጅነር ጌታሁን መኩርያን በጤና ጥበቃ ሚኒስቴር መ/ቤት ስም አመሰግናሁ ብለዋል ዶ/ር አሚር።

Write a Reply or Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *