loading
የኢትዮጵያ ህዝብ አርበኞች ግንባር ከግንቦት 7 ጋር በይፋ መለያየቱን አስታወቀ

አርትስ 14/01/2011
የኢትዮጵያ ህዝብ አርበኞች ግንባር በትናንትናው ዕለት በሰጠው መግለጫ ከግንቦት 7 ጋር መለያየቱን ይፋ አድርጓል። ነገር ግን ንቅናቄው የተሰጠው መግለጫ ህጋዊነት የጎደለው ነው ብሏል፡፡
የግንባሩ ሰብሳቢ አቶ መንግስቱ ወልደስላሴ እንደተናገሩት፥ ከግንቦት ሰባት ጋር በአመራር አሰጣጥ እንዲሁም በፋይናስ አሰራር ላይ ባለ ክፍተት ምክንያት ለመለያየት መወሰናቸውን አስታውቀዋል።
የአርበኞች ግንቦት ሰባት የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ አምሳሉ ፀጋ ናቸው ንቅናቄው ከየትኛውም ጥምረት አልተለየም ያሉት፡፡

Write a Reply or Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *