loading
በኢትዮጵያ እና በብሪታኒያ መካከል ያለው ግኙነት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የብሪታኒያ የፓርላማ ልኡካን ቡድን አባላት ተናገሩ

በኢትዮጵያ እና በብሪታኒያ መካከል ያለው ግኙነት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የብሪታኒያ የፓርላማ ልኡካን ቡድን አባላት ተናገሩ

የልኡካን ቡድኑ አባላት ከህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ተሰፋዬ ዳባ ጋር ተወያይተዋል፡፡

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንደገለፀው በውይይቱ ወቅት የብሪታኒያ የፓርላማ ልኡክ አባላቱ ጉብኝት አላማ የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት ለማጠናከር እና በፓርላማዎቹ መካከል የሀሳብ ልውውጥ ለማድረግ ያለመ መሆኑን ተናግዋል፡፡

የልኡካን ቡድኑ የኢትዮጵያ መንግስት የፖለቲካ ምህዳሩን ለማስፋት እያከናወናቸው ያሉ ተግባራትን አድንቀዋል፡፡

የቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢው አቶ ተስፋዬ ዳባ በበኩላቸው የኢትዮጵያ እና ብሪታኒያ ግንኙኘት እ.ኤ.አ ከ1897 አም ጀምሮ የተመሰረተ መሆኑን አውስተው በባህል፣ በምጣኔ ሀብትና በፖለቲካ ጉዳዮች ዙሪያ በትብብር እየሰሩ እኝደሚገኙ ተናግረዋል፡፡

የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት አጠናክሮ ለማስቀጠል እና የፓርላማ አባለቱን አቅም ለማሳደግ ብሪታኒያ በአቅም ግንባታ በኩል ድጋፍ እንድታደርግ ሰብሳቢው አቶ ተስፋዬ ጠይቀዋል፡፡

Write a Reply or Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *