loading
ብሬንዳን ሮጀርስ የሌስተር አሰልጣኝ ለመሆን ተቃርበዋል ተባለ

ብሬንዳን ሮጀርስ የሌስተር አሰልጣኝ ለመሆን ተቃርበዋል ተባለ

የቀድሞው የሊቨርፑል አሰልጣኝ ብሬንዳን ሮጀርስ የፕሪምየር ሊጉ ተሳታፊ ሌስተር ሲቲ ክላውድ ፑኤልን ካሰናበተ በኋላ፤ ስማቸው ከክለቡ ጋር ከተያያዙ አሰልጣኞች መካከል ይጠቀሳሉ፡፡

የሚያሰለጥኑት ክለብ ሴልቲክም ሮጀርስ ከሌስተር ጋር እንዲነጋገሩ መልካም ፍቃዱን ሰጥቷቸዋል ሲል ቢቢሲ አስነብቧል፡፡

ሰሜን አየርላንዳዊው አሰልጣኝ በግላስጎው የሰባት የውድድር ዓመት ቆይታው ሰባት የስኮትላንድ ዋንጫዎችን አሳክተዋል፡፡

የሴልቲክ አንደኛ ቡድን አሰልጣኝ ጆን ኬነዲ ክለቡ በስኮትላንድ ፕሪሚየርሽፕ ነገ ከኸርትስ ጋር ላለበት  ጨዋታ ይመሩታል ተብሏል፡፡

Write a Reply or Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *