loading
ካይሮ ውስጥ በደረሰ የባቡር አደጋ የሞት እና የአካል ጉዳት ደርሷል ተባለ፡፡

ካይሮ ውስጥ በደረሰ የባቡር አደጋ የሞት እና የአካል ጉዳት ደርሷል ተባለ፡፡

በማእከላዊ ካይሮ በሚገኘው ራምሴስ የባቡር ጣቢያ በአንድ ባቡር ላይ በተነሳ እሳት 25 ሰዎች ሲሞቱ  ሀምሳ የሚሆኑት ደግሞ የመቁሰል አደጋ ደርሶባቸዋል፡፡

በአካባቢው የነበሩ የዓይን እማኞችን ጠቅሶ ሮይተርስ እንደዘገበው እሳቱ ከመቀስቀሱ በፊት ከፍተኛ የፍንዳታ ድምጽ ተሰምቷል፡፡

ሰዎቹ አክለውም ባቡሩ በፍጥነት ተንቀሳቅሶ  ከአጥር ጋር ከመጋጨቱ የፍንዳታ ድምፅ መስማታቸውን እና ወዲያው የእሳት ቃጠሎ መከሰቱን ተናግረዋል፡፡

ከተከሰተው አደጋ አንፃር የሟቾች ቁጥር ሊጨምር እንደሚችል የግብፅ መገናኛ ብዙሀን  በዘገባቸው አስነብበዋል፡፡

በግብፅ የባቡር አደጋ የተለመደ ሲሆን ነዋሪዎች መንግስት ችግሩን ለመቅረፍ ጥረቱ አናሳ ነው በማለት በተደጋጋሚ ወቀሳ ያቀርባሉ፡፡

 

መንገሻ ዓለሙ

Write a Reply or Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *