SportSports

ማንችስተር ዩናይትድ እና ፖርቶ ሩብ ፍፃሜውን ተቀላቅለዋል

ማንችስተር ዩናይትድ እና ፖርቶ ሩብ ፍፃሜውን ተቀላቅለዋል

ትናንት ምሽት በተደረጉ ሁለት የአውሮፓ ቻምፒዮንስ ሊግ ጨዋታዎች በመጀመሪያው ዙር  የተመዘገቡ ውጤቶች ተቀልብሰዋል፡፡

ፓርክ ደ ፕረንስ ላይ ከፒ.ኤስ.ጂ ጋር የተጫወተው ማንችስተር ዩናይትድ በሮሜሉ ሉካኩ ሁለት እና ራሽፈርድ የፍፁም ቅጣት ምት ጎል 3 ለ 1 ድል አድርጎ፤ በድምር ውጤት 3 ለ 3 አቻ ቢለያይም ዩናይትድ ከሜዳ ውጭ የተሻለ የግብ መጠን ያስመዘገበ በመሆኑ ሩብ ፍፃሜውን ተዋህዷል፡፡

ዩአን ቤርናት ለፓሪሱ ቡድን የማስተዛዘኛዋን ግብ አስቆጥሯል፡፡

በተመሳሳይ ሰዓት ፖርቶ በእስታዲዮ ዶ ድራጋዎ ሮማን አስተናግዶ 3 ለ 1 በመርታት ወደ ተከታዩ ዙር ማለፉን አረጋግጧል፡፡

ሱአሬስ፣ ማሬጋ እና ቴሌስ ሲያስቆጥሩ፤ የሪማን ግብ አምበሉ ዴ ሮሲ በፍፁም ቅጣት ምት ከመረብ አገናኝቷል፡፡

እስካሁን ቶተንሃም.፣ አያክስ፣ ማንችስተር ዩናይትድ እና ፖርቶ ሩብ ፍፃሜውን ተዋህደዋል፡፡

ቀጣይ ሳምንት ቀሪዎቹ አራት ቡድኖች የሚለዩ ሲሆን ማክሰኞ ዩቬንቱስ ከ አትሌቲኮ ማድሪድ እና ማንችስተር ሲቲ ከ ሻልከ 04 እንዲሁም ዕረቡ ባርሴሎና ከ ሊዮን እና ባየርን ሙኒክ ከ ሊቨርፑል ይጫወታሉ፡፡

Related Articles

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Back to top button