EthiopiaHealth

ከ121 በላይ የጤና ባለሙያዎች ለጌዲዮ ተፈናቃዮች ድጋፍ ማድረግ ተልከዋል ተባለ፡፡

ከ121 በላይ የጤና ባለሙያዎች ለጌዲዮ ተፈናቃዮች ድጋፍ ማድረግ ተልከዋል ተባለ፡፡

የጤና ሚኒስቴር ለጌዲዮ ዞን ተፈናቃዮች ድጋፍ የሚሰጡ የጤና ባለሙያዎችና የተለያዩ መድሃኒቶች እንዲሁም ሌሎች ግብአቶችን ወደ ስፍራው ልኳል፡፡

የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታዋ ዶክተር ሊያ ታደሰ እንደገለፁት ካሁን በፊት ከክልል 10 ሐኪሞች ፣ 10 ነርሶች፣ 5 የአካባቢ ጤና ባለሙያዎች እና 5 የኢፒዲሞሎጂ ባለሙያዎች ወደ ስፍራው ተልከዋል፡፡

የህብረተሰብ ጤና አደጋ ቁጥጥር ቅኝቶችና ዳሰሳዎች እንዲሁም  የገንዘብ ድጋፍም ተደርጓል፡፡

በዚህኛው ፕግራም ከአዲስ አበባ የተውጣጡ አምስት ሐኪሞች እና 26 ነርሶች እንዲሁም መድኃኒቶችና ሌሎች ግብዓቶች ከኢትዮጵያ መድሀኒት አቅራቢ ኤጀንሲ ወጪ ሆነው ወደ ስፍራው ተልከዋል ብሏ ሚኒስቴሩ፡፡

ሚኒስትር ዴኤታዋ ወደ ስፍራው ካቀኑት ከ121 በላይ የጤና ባለሙያዎች በተጨማሪ የተለያዩ መጠን እና አይነት ያላቸው መድሃኒቶች መላካቸውንና ይህ መሰሉ ተግባር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል፡፡

Related Articles

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Back to top button