loading
ፕሬዚዳንት ሣህለወርቅ የክበበ ጸሀይ ህጻናት ማሳደጊያ ማዕከልን እየጎበኙ ነው

ፕሬዚዳንት ሣህለወርቅ የክበበ ጸሀይ ህጻናት ማሳደጊያ ማዕከልን እየጎበኙ ነው

የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ሣህለ ወርቅ ዘውዴ የክበበ ጸሀይ ህጻናት ማሳደጊያ ማዕከልን እየጎበኙ መሆናቸውን የፕሬዝዳንት ፅህፈት ቤት አስታወቋል፡፡

ማዕከሉ በ1956 የተመሰረተ ሲሆን በአሁኑ ወቅት 200 የሚደርሱ ወላጅ አልባ እና አካል ጉዳተኛ ህጻናትን ተቀብሎ በመንከባከብ ላይ ይገኛል።

ክበበ ጸሀይ የህጻናት ማሳደጊያ ማዕከል ህፃናትን ዘጠኝ አመት እስኪሞላቸው ድረስ እንደሚያሳድግና ከዘጠኝ አመታቸው በኋላ ወደ ሌሎች ማዕከላት እንደሚልክ ተነግሯል፡፡

ክበበ ጸሀይ አሁን ያለበት ቦታ  ከአንጋፋዉ  ደራሲ ሀዲስ አለማየሁ የተበረከተ  መኖሪያ ቤታቸዉ ነበር ፡፡

 

Write a Reply or Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *