loading
ባለፈው መስከረም ከነትጥቃቸው ወደ ጠቅላይ ሚንስትር ጽሕፈት ቤት የገቡ ወታደሮች ፍርዳቸው በይግባኝ ተቀነሰላቸው

ባለፈው መስከረም ከነትጥቃቸው ወደ ጠቅላይ ሚንስትር ጽሕፈት ቤት የገቡ ወታደሮች ፍርዳቸው በይግባኝ ተቀነሰላቸው

ውሳኔውን ያሳለፈው በመከላከያ ፍትሕ መምርያ መከላከያ ወታደራዊ ፍርድ ቤት የይግባኝ ሰሚ ችሎት ነው፡፡

ከ200 በላይ ኮማንዶዎች በወቅቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት መግባታቸው ሲታወስ፣ 66 አባላት ግን በወታደራዊ ፍርድ ቤት የእስር ፍርድ ሲተላለፍባቸው የተቀሩት አስተዳደራዊ ውሳኔ እንደተላለፈባቸው በወቅቱ ተገልጾ ነበር፡፡

14 አመት የነበረው ከፍተኛው የእስር ጣሪያ ወደ 10 ዝቅ ሲደረግ፣ ዝቅተኛው የእስር ጊዜ 5 አመት ተደርጎላቸዋል ነው የተባለው፡፡

ፍርደኞቹ ከፍርድ በኋላ ከታጠቅ እስር ቤት ወደ ሸዋ ሮቢት እና ቃሊቲ መዛወራቸውን እና በሕጉ መሠረት ፍርደኞቹ የእስር ዘመናቸውን ጨርሰው ወደ ሠራዊቱ የመመለሳቸው ዕድል አናሳ መሆኑን ሪፖርተር ዘግቧል፡፡

 

Write a Reply or Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *