loading
ዕጣ የወጣባቸው የ40/60 የጋራ መኖሪያ ቤቶች ለባለዕድለኞች እንዳይተላለፉ የቀረበው የዕግድ ጥያቄ ተቀባይነት አላገኘም ተባለ 

ዕጣ የወጣባቸው የ40/60 የጋራ መኖሪያ ቤቶች ለባለዕድለኞች እንዳይተላለፉ የቀረበው የዕግድ ጥያቄ ተቀባይነት አላገኘም ተባለ

ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር ቅድሚያ ቤት ለማግኘት መቶ በመቶ ክፍያ  ፈጽመው የተዋዋሉ 98 ግለሰቦች ያቀረቡትን ክስ የመረመረው፣ የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የቀረበለትን ክስ መርምሮ ሦስት ትዕዛዞች ሰጥቷል፡፡

ፍርድ ቤቱ በመጀመርያ የሰጠው ትዕዛዝ ክስ የቀረበባቸው የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስቴር፣ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክና የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ቤቶች ልማት ኢንተርፕራይዝ ለቀረበባቸው ክስ ግንቦት 29 ቀን 2011 ዓ.ም. ምላሽ እንዲሰጡ ነው፡፡ ሌላው ሁለቱ ወገኖች (ከሳሾችና ተከሳሾች) ሰኔ 10 ቀን 2011 ዓ.ም. በችሎት ቀርበው ክርክር እንዲያደርጉ ሲሆን፣

ሶስተኛው ደግሞ የይዞታ ማረጋገጫ ሰነድ (ካርታ) የፍርድ ቤቱ ክርክር እስከሚጠናቀቅ ድረስ ዕጣ ለወጣላቸው ግለሰቦች እንዳይሰጥ ዕግድ ጥሎበታል ሪፖርተር እንደዘገበው፡፡

Write a Reply or Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *