loading
ኢትዮጵያ ቡና ለምርጡ ደጋፊው ክብር ሰጥቷል

በትላንትናው ምሽት በዋቢ ሸበሌ ሆቴል የኢትዮጵያ ቡና ስፖርት ክለብ ቤተሰብ አንድ ወዳጃቸውን ግን እንደ ብዙ የሚመለከቱትን የልብ የሆነ ሰዋቸውን እና ባለውለታ እስከመባል የደረሰውን የደጋፊዎች ፊትአውራሪ አዳነ ሽጉጤ ምስጋና ሰጥተዋል!!!

የኢትዮጵያ ቡና ምልክት የሚል ቦታ የተሰጠው፤ ለረጅም ዓመት በአዲስ አበባ ስታዲየም ሚስማር ተብሎ በሚጠራው ቦታ ላይ በማስጨፈር ክለቡን ሲደግፍ የነበረው አዳነ ሽጉጤን በምሽቱ በርካታ ተጋባዥ እንግዶች ፣ የክለቡ አመራሮች እና ቡናማ ደጋፊዎች ፤ አርቲስቶች እና የእግር ኳስ ቤተሰቦች በተገኙበት ለኢትዮጵያ ቡና ስላበረከተው ነገር ሁሉ ክብር እና ውዳሴ ይገባሃል በማለት በወዳጆቹ ታጅቦ ተመስግኗል፡፡

አዳነ ሽጉጤ ከተወዳጅ የክለብ ድጋፉ በተጨማሪ የብሔራዊ ቡድኖች ጨዋታዎች ላይ ከሌሎች ክለቦች ደጋፊዎች ጋር በመተባበር ደመቅ ያለ ድጋፉን ሲሰጥ ነበረ፡፡

አዳነ የሚስማር ገዥነቱን ለማመልከት ቡናማ ወንድሞቹ ፡

‹‹የተቆላ ቡና እሚመስለው ፊቱ

አደነ ሽጉጤ ሚስማር ላይ ነው ቤቱ›› እያሉ አዚመውለታል፡፡

ይህ ሰው ከ22 ዓመታት በላይ በእግር ኳሱ የድጋፍ አበርክቶ ቆይታ እንደነበረው ይነገራል፡፡

Write a Reply or Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *