loading
አርሰናል ወደ አራተኛ ደረጃ ከፍ ብሏል

ትናንት ምሽት የእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ የ34ኛ ሳምንት መርሀግብር መቋጫ ግጥሚያ ዲን ኮርት ላይ በዋትፎርድ እና አርሰናል መካከል ተካሂዶ መድፈኞቹ 1 ለ 0 በሆነ ጠባብ ውጤት በመርታት ደረጃቸውን አሻሽለዋል፡፡

በምሽቱ ጨዋታ አርሰናች አሸናፊ የሆኑበትን ብቸኛ ግብ የባለሜዳዎቹ ግብ ጠባቂ ቤን ፎስተር የሰራውን ስህተት ተጠቅሞ ጋቦናዊው ፔር ኤምሪክ ኦባማያንግ አስቆጥሯል፡፡

ከግቧ መቆጠር አንድ ደቂቃ በኋላ የዋትፎርድ አምበል ትሮይ ደኒ በአርሰናሉ ሉካስ ቶሬራ ላይ በሰራው ጥፋት በዕለቱ አርቢትር ክሬግ ፓውሰን ቀጥታ ቀይ ካርድ ተመልክቷል፡፡

በ10 ተጫዋቾች 80 ደቂቃዎችን የተጨወቱት ባለሜዳዎቹ በርካታ የግብ ዕድሎችን መፍጠር ቢችሉም ግብ ሳያስቆጥሩ ወጥተዋል፡፡

መድፈኞቹም ቢሆኑ ተጨማሪ ግቦችን አስቆጥረው ማሸነፍ የሚችሉባቸውን አጋጣሚዎች አልተጠቀሙባቸውም፡፡

ድሉን ተከትሎ አርሰናል ከቼልሲ ዕኩል 66 ነጥቦችን በመያዝ በግብ ክፍያ በልጦ አራተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል፡፡

በፕሪምየር ሊጉ ከዋንጫው አሸናፊ ፉክክር ዕኩል በሚቀጥለው የውድድር ዓመት የአውሮፓ ቻምፒዮንስ ሊግ ተሳትፎ ለማግኘት የሚደረገው ትግል አጓጊ ነው፡፡

Write a Reply or Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *