loading
የሴቶችን ተጠቃሚነት እና እኩልነትን ለማረጋገጥ የተቀናጀና ትብብርን መሰረት ያደረገ እንቅስቃሴ” ፕሬዚዳንት ሣህለ ወርቅ ዘውዴ

በኢትዮጵያ የሴቶችን ተጠቃሚነት እና እኩልነትን ለማረጋገጥ የሚከናወኑ ተግባራትን ውጤታማ ለማድረግ የተቀናጀና ትብብርን መሰረት ያደረገ እንቅስቃሴ እንደሚያስፈልግ ፕሬዚዳንት ሣህለ ወርቅ ዘውዴ አስገነዘቡ።

“መተባበር ለላቀ ውጤት” በሚል ርዕስ የተዘጋጀው እና በሥርዐተ ጾታ እኩልነት እና ሴቶችን በማብቃት ዙሪያ የሚሰሩ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የውይይት መድረክ በአፍሪካ ኢኮኖሚክ አዳራሽ ዛሬ ረፋድ ላይ ሲጀመር ፕሬዚዳንቷ እንዳሉት በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ የተፈጠረውን መልካም እድል በአግባቡ በመጠቀም በተወስነ የስራ ዘርፍ ላይ ያተኮሩ፣ ድግግሞሽን ያስወገዱ እና መተባበርን ያስቀደሙ ስራዎችን ማከናወን ይገባል ብለዎል።
በውይይት መድረኩ በሥርዐተ ጾታ እኩልነት እና ሴቶችን በማብቃት ዙሪያ ከሚሰሩ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የተወከሉ ከ200 በላይ ተሳታፊዎች ተካፍለዎል  ሲል የፕሬዝዳንት ፅህፈት ቤት ቢሮ ገልጿል።

Write a Reply or Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *